ETHIOPIAN ENTERPRISES DEVELOPMENT

Empowering Manufacturing SMEs for National Economic Transformation and Societal Prosperity !

አቶ ጳውሎስ በርጋ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር

አምራች ዘርፉን ለሚደግፉ የፌዴራልና የክልል ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው::

“አምራች ዘርፉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ  እንዲሆን ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን መፍጠር ያስፈልጋል!”

አቶ ጳውሎስ በርጋ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር

አምራች ዘርፉን ለሚደግፉ የፌዴራልና የክልል ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው::

EED ሐምሌ 21/2017 ዓ.ም (አዳማ)

በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንስ ፕሮጀክት ኮንሱል ከተባለ አማካሪ ድርጅት ጋር በመተባበር አምራች ዘርፉን ለሚደግፉ የፌዴራልና የክልል ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ነው::

የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የከፈቱት የልማት መስሪያ ቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ጳውሎስ በርጋ እንደተናገሩት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ እንዲኖረን ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ  ባለሙያዎች መፍጠር ያስፈልጋል::

በአምራች ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችሉና በጥናት የተለዮ ሰነዶች መዘጋጀታቸውን የገለፁት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ስልጠናው የባለሙያዎችን ክፍተትና ፍላጎት መሰረት ያደረገ በመሆኑ አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል::

ለአምራች ዘርፉ የተመቻቹ እድሎችን ወደተግባር በመለወጥና በመደገፍ ኢንተርፕራይዞችን ማብቃትና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ መስራት እንደሚጠይቅም አቶ ጳውሎስ ገልፀዋል::

የንግድ ስራ እቅድ አዘገጃጀት፣ እሴት ሰንሰለት ልማት፣ ፋይናንስ አቅርቦት አጋርነት፣ ንግድ ልማት ክህሎት እና ስትራቴጅካዊ አጋርነት እና የባለድርሻ  አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ዙርያ ስልጠና የሚሰጥባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው::

#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት

ለተጨማሪ መረጃ ፡-

#ድረ_ገጽ: https://www.manuf-sme.gov.et

#ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/Ethiopianenterprisedevelopment

#ቴሌግራም፡ https://t.me/ethiopianenterprisedevelopment

#ዩትዩብ፡ https://youtube.com/@ethiopiaenterprise

#ኢሜል: ethiopianenterprise@gmail.com

News